Sunday, February 18, 2018

የሙዝ ፍራፍሬ ለጤንነታችን የሚሰጠው ጥቅሞች!


ይህን ካነበቡ በኋላ ለሙዝ ያለዎት አመለካከት በእጅጉ ይቀየራል::የሚለን ሳይቴክ ነው ለመረጃው እያመሰገንኩኝ ለውድ ተከታዮቼ እንሆ ይህንን መረጃ ብያለሁ።ሙዝ ሶስት የተፈጠሮ ስኳሮችን (ማለትም ሱክሮስ፣ ፍሩክቶስ እና ግሉኮስ) ከፋይበር ጋር አጣምሮ ይዟል:: እነዚህም የሰዉነታችንን ኃይል ከፍ የማድረግ አስተዋፅኦ አላቸው::ጥናቶች እንዳረጋገጡት ከዘጠና ደቂቃ ከባድ የአካል እንቅስቃሴ በኋላ 2 ሙዝ የሚመገቡ ስፖርተኞች እንደገና ኃይላቸውን ማደስ ይችላሉ:: ለዚህም ነው – በዓለማችን ታላላቅ ስፖርተኞች ዘንድ ‘ሙዝ’ ተወዳጅ እና ተመራጭ ፍራፍሬ የሆነው::ይህ ብቻ አይደለም: ሙዝ የሚመገቡ ሰዎች የተለያዩ ህመሞችና ከባድ ሁኔታዎችን የመከላከል አቅማቸው እጅግ በጣም ከፍ ያለ ነው:: ከብዙ በጥቂቱ የሚከተሉትን ጥቅሞች ያስገኛል፤1. የአንጀት ቁስለትን ይከላልከላል
2. ከሀንግ ኦቨር (HANG OVER) በፍጥነት ያላቅቃል
3. አእምሮ እንዲነቃቃ ያግዛል
4. የደም ማነስ ችግርን ያስዎግዳል
5. የሰዉነት ሙቀትን ለመቆጣጠር ይረዳል
6. የድብርት ስሜትን ያስዎግዳል፤ እንዲሁም ራስን ለማረጋጋት ይጠቅማል7. ለደም ግፊትን ያስታግሳል
8. የሰገራ ድርቀትን ይከላከላል
9. የወር አበባን ተከትሎ የሚመጣ የስሜት መለዋወጥን ይቀንሳል
10. ቃርን ያስወግዳል
11. ሌላው በጣም የሚገርመው ከወባ ትንኝ ንክሻ ይከላከላል (ቆዳዎትን በልጣጩ ከቀቡት) – ይቺኛዋ መረጃ በተለይ በሞቃታማው የአገራችን ክፍል ለምትገኙ ትሁንልን ብለናል!!በተጨማሪ:
አንድ ሙዝ ከሌላ ፍራፍሬ ጋር ስናወዳድረው ለምሳሌ ከአንድ አፕል (an apple) ጋር ብናወዳደር:-
አንድ ሙዝ በውስጡ የአፕልን
• 4 እጥፍ ፕሮቲን
• 2 እጥፍ ካርቦሃይድረት
• 3 እጥፍ ፎስፈረስ
• 5 እጥፍ vit A እና ብረት(IRON)• እንዲሁም ከፍተኛ የሆነ ፖታሽየም የያዘ ነው::(ለሌሎች share ማድረግዎን እንዳይዘነጉ!)

Source MEREJA 24.INFO

Friday, January 19, 2018

ልክ ያጣው የእነ ገብረ እግዚያብሔር እብሪት(በጌታቸው ሺፈራው)


አስቻለው ደሴ የፌደራል ፖሊስ አባል ነበር። አማራ በሰበብ በሚታሰርበትና በሚከሰስበት ግንቦት 7 አባል ነህ ተብሎ ታሰረ። የተለመደውና የሌለው የ"ሽብር" ክስ ተመስርቶበታል። የታሰረው ደግሞ የአማራ ወጣቶች ዘራቸውን እንዳይተኩ ከሚኮላሹበት ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ነው። እንደሌሎቹ ወንድሞቹ አስቻለው ደሴንም ብልቱ ላይ ሁለት ሊትር ሀይላንድ ውሃ አንጠልጥለው ዘሩን እንዳይተካ አድርገውታል። ጆሮውንም ጎድተውታል። ለዚህ ሁሉ ቁስሉ ምንም አይነት የህክምና እርዳታ አላገኘም። በክሱና በማንነቱ ምክንያት ህክምና ተከልክሏል። ጥጋበኞች ላቆሰሉት፣ ለጎዱት አካልና መንፈሱ ምንም አይነት ህክምና አላገኘም።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ ማዕከላዊ የደረሰበትን አሰቃቂ በደል በቃል ሊገልፅ ሲል "በፅሑፍ አቅርብ" ተባለ። አስቻለው ደሴ ግን የተፈፀመበትን ቢያንስ በችሎቱ የታደሙት ወገኖቹ ያዩለት ዘንድ ሱሪውን አውልቆ "የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረደኝ" አለ። ችሎቱን የታደሙት አነቡ፣ ከአስቻለው በምሬት እየተናገረ በችሎት የነበሩት በተለይም የሴቶች ሲቃም አጀበው። በፅሑፍ አቅርብ ያሉት ዳኞች፣ ያጀቡት ፖሊሶች በአስቻለው የሰቆቃ ድምፅ ፀጥ አሉ። ይሰማ የነበረው የእሱ የሰቆቃ ጩኸትና የታዳሚዎች ሲቃ ብቻ ነበር።
አስቻለው ደሴ ይህን ሰቆቃ ተናግሮ ወደ ቂሊንጦ ሲመለስ፣ ሌላ ቅጣት ነበር የጠበቀው። ከቃጠሎው በኋላ በግዳጅ በእስረኛ ጉልበት ወደተሰራው ዞን 5 ተቀየረ። ዞን 5 ጥብቅ ቁጥጥርና አፈና ያለበት እስር ቤት ነው። የቂሊንጦ እስር ቤት ኃላፊዎች ምንም በማያገባቸው አስቻለውን ጨምሮ በርካቶችን ፍርድ ቤት በሚናገሩት ይደበድቧቸዋል። ወደ ጨለማ ቤት ይልኳቸዋል። የአሳሪዎቹ እብሪት ግን በዚህ ግን አላበቃም።
የአስቻለው ቤተሰብ የሆኑ ቄስ ይህን መከረኛ ወጣት ለመጠየቅ ከአማራ ክልል ወደ ቂሊንጦ ይሄዳሉ። እስር ቤቱ በር ላይ ግን ያልጠበቁት ይገጥማቸዋል። ጥምጣማቸውን ካላወለቁ ወደ እስር ቤቱ እንደማይገቡ ይነገራቸዋል። ቄሱ ቢለምኑ የሰማቸው አላገኙም። አሳሪዎቹ የቄስ ማንነትንም ወደ ኋላ ያያሉ፣ በመጡበት አካባቢ ይመዝኗቸዋል፣ ያዋርዷቸዋል፣የእስረኛውን ማንነት ጋርም ያያይዙታል።
ቄሱ ሰቆቃ የደረሰበትን አስቻለውን ለመጠየቅ ሲሉ ቆባቸውን አውልቀው ገቡ። የተፈፀመባቸውን አስፀያፊ ተግባርም ለአስቻለው አጫወቱት። አስቻለው ለምን እንዲህ ይበድሉናል ብሎ በምሬት ሲናገር ከጎኑ የቆመው ጥበቃ ፖሊስ እየሰማ ነበር። ይህም ወንጀል ሆኖ ለእነ ገብረ እግዚያብሔር ተነገራቸው። ገብረ እግዚያብሔር የተባለ ፖሊስ እግዚያብሔርን የማይፈራ ከቂሊንጦ "ኃላፊዎች" መካከል አንዱ ነው። ቄሱ ቆባቸውን አውልቀው እንዲገቡ መገደዳቸው ሳይበቃ፣ ይህ መደረግ አልነበረበትም አለ ተብሎ አስቻለውን አስደብድቦ ጨለማ ቤት እንዲገባ አድርጓል። ያ ሁሉ በደል የተፈፀመበት አስቻለው በቤተሰቦቹ እንዳይጠየቅ ተከልክሏል። ማዕከላዊ በተፈፀመበት ድብደባ ቁስሉ ሳይጠግግና ህክምና ሳያገኝ አሁንም እየተደበደበ ነው። የእነ ገብረ እግዚያብሔር እብሪት ልክ አጥቷል!
ምንጭ ጌታቸው ሺፈራው ከፌስቡክ ገልፅ 

Wednesday, December 20, 2017

የኦሕዴድና ብአዴን የፓርላማ አባላት ስብሰባ አንሳተፍም አሉ


(ኢሳት ዲሲ--ታህሳስ 11/2010) በኢትዮጵያ ፓርላማ የኦሕዴድና ብአዴን አባላት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በምክር ቤት ተገኝተው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ካልሰጧቸው በመደበኛ ስብሰባዎች አንሳተፍም አሉ።
የኦሕዴድና የብአዴን የሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት ሀገሪቱን ስጋት ላይ በጣላት ብሄር ተኮር ግጭትና የፖለቲካ ቀውስ ላይ አቶ ሃይለማርያም ማብራሪያ እንዲሰጡ ጥያቄ አቅርበዋል።
አባላቱ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሱት በተወከሉባቸው የፖለቲካ ድርጅቶች ውይይት ካካሄዱ በኋላ ነው።
በኢትዮጵያ ያለው ቀውስ ከፖለቲካ ፓርቲ ሽኩቻ ወደ ፓርላማ አባላትም ተሸጋግሯል።
የወቅቱ የኢትዮጵያ ሁኔታ ያሳሰባቸው የኦሕዴድና የብአዴን ተወካይ የሆኑ የምክር ቤት አባላት በመደበኛ ስብሰባ ማሳተፍ ማቆማቸውን ነው የገለጹት።
ምክንያታቸው ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ሃገሪቱን ስጋት ላይ በጣለው ብሔር ተኮር ግጭትና የፖለቲካ ቀውስ ላይ መጀመሪያ ማብራሪያ ይስጡን በሚል ነው።
እናም የምክር ቤቱ አባላት ያቀረቡት ጥያቄ ምላሽ አግኝቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርላማ እስኪገኙ ድረስ መደበኛ ስብሰባዎችን አንሳተፍም ብለዋል።--የኦሕዴድና የብአዴን ተወካይ የፓርላማ አባላት።
አባላቱ ላቀረቡት ጥያቄ ከምክትል አፈ ጉባኤዋ ወይዘሮ ሽታዬ ምናለ ምላሽ እየተጠበቀ መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ በዘገባው አመልክቷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞም ባለፈው ሳምንት ሀሙስና ትላንት ማክሰኞ መካሄድ የነበረበት የፓርላማው መደበኛ ስብሰባ አለመካሄዱ ነው የተነገረው።
በምክር ቤቱ የአሰራርና የአባልነት ስነምግባር ደንብ መሰረት የፓርላማ አባላት ጠቅላይ ሚኒስትሩን በወር አንድ ጊዜ ጠርተው ማብራሪያ መጠየቅ ይችላሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ደንብ መሰረት በአመት 2 ጊዜ ዝርዝር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤቱ የማቅረብም ግዴታ አለባቸው።
በፓርላማ አባላቱ ጥያቄ መሰረት አፈ ጉባኤዋ ወይዘሮ ሽታዬ ምናለ ምላሽ ባይሰጡ ስለሚከተለው ሁኔታ በሕጉ የተቀመጠ ነገር የለም።
ጉዳዩን በተመለከተ ከሪፖርተር ጥያቄ የቀረበለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል።

ምንጭ ኢሳት ዜና 

Sunday, August 27, 2017

በሳዑዲ አረቢያ ያሉ ኢትዮጵያውያን በግዳጅ እንዳይባረሩ ጥሪ ቀረበ

BBN news August 26, 2017
በሳዑዲ አረቢያ ያለ መኖሪያ ፈቃድ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከሀገሪቱ እንዳይባረሩ ጥሪ ቀረበ፡፡ የሳዑዲ አረቢያ መንግስት ስደተኞቹን ለማባረር መግለጫ ማውጣቱን ተከትሎ ድምጹን ያሰማው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የሆነው ሂውማን ራይትስ ዎች፣ መንግስት በስደተኞቹ ላይ የማባረር እርምጃ እንዳይወስድ ጠይቋል፡፡ የሳዑዲ አረቢያ መንግስት በሀገሪቱ ያለ ህጋዊ ወረቀት የሚኖሩ ስደተኞች እንዲወጡ የሶስት፣ ቀጥሎም ሁለት ጊዜ የአንድ ወር ቀነ ገደብ መስጠቱ ይታወሳል፡፡ መንግስት ከትላንት በስቲያ እንዳስታወቀው፣ ስደተኞችን በኃይል የማስወጣት እርምጃ ሊወሰድ ነው፡፡
የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የሆነው ሂውማን ራይትስ ዎች፣ ሳዑዲ ይፋ ያደረገችውን ቀጣይ እርምጃ የምትፈጽም ከሆነ፣ ከግማሽ ሚሊዬን በላይ ወረቀት የሌላቸው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የእርምጃው ሰለባ ይሆናሉ፡፡ በኃይል ሊወሰድ የሚችለውን እርምጃ ተከትሎ በርካቶች ሊጎዱ እንደሚችሉ ያስገነዘበው የሰብዓዊ መብት ተሟጋጅ ድርጅቱ፣ በተለይ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የፖለቲካ ጠብ ያላቸው ስደተኞች ይበልጥ ተጎጂ ሊሆኑ እንደሚችሉም አስጠንቅቋል፡፡ በሳዑዲ አረቢያ የኢኮኖሚ ስደተኞች የመኖራቸውን ያህል የኢትዮጵያ መንግስትን ሽሽት ወደ ሳዑዲ የተሻገሩ መኖራቸውን ያወሳው ድርጅቱ፣ ሳዑዲ ያለችውን እርምጃ የምትወስድ ከሆነ፣ የእነዚህ ስደተኞች ዕጣ ፈንታ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ገልጿል፡፡
ስደተኞቹ በኃይል ተገድደው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የሚደረግ ከሆነ፣ በኢትዮጵያ ለህይወታቸው አስጊ የሆነ ነገር እንደሚጠብቃቸው የገለጸው የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ፣ ምናልባትም የኢትዮጵያ መንግስት ግድያን ጨምሮ መሰል እርምጃዎችን ሊወስድባቸው እንደሚችል ከወዲሁ ስጋቱን ገልጿል፡፡ ከዚህ ቀደም ከሳዑዲ አረቢያ በኃይል ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ከተደረጉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች መካከል በመንግስት ግድያ የተፈጸመባቸው መኖራቸውንም ሂውማን ራይትስ ዎች በመግለጫው አትቷል፡፡ ስለ ስደተኞች ብሎ የሳዑዲ አረቢያን መንግስት የሚማጸነው የድርጅቱ መግለጫ፣ ከሳዑዲ ባለስልጣናት በኩል እስካሁን ምላሽ አላገኘም፡፡ ሳዑዲ ያወጣችውን የምህረት ቀነ ገደብ ተከትሎ፣ ከ50 ሺህ የማይበልጡ ወረቀት የሌላቸው ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መግባታቸው በመንግስት በኩል ሲገለጽ ቆይቷል፡፡

source BBN news August 26,2017

Monday, December 5, 2016

የ2016የወንዶች የእግር ኳስ ውድድር በስቮልቫር ቡድን አሽናፊነት በድል ተጠናቀቀ

በለፈው  ቅዳሜ ዕለት ማለትም 3/12/2016  በተደረገው  የመጨረሻው  የመዝጊያው  ውድድር  የስቮልቫር  ቡድን በዕለቱ ከተሳተፉት ቡድኖች ሁሉ የላቀ ቴክኔክ እና ዜዴ በመጠቀም ለተመልካቹና ለደጋፊው የተሻለ የኳስ ውበት የላቀ የጨዋታ የቡድን ስራውን በ አግባቡ በመጠቀም በማሳየት አስመስክሯል ይህም የሚያሳየው በቡድኑ ውስጥ የነበረውን የዲሲፒልን   የእርስበእርስ የመከባበር  የመመካከር  ውጤት ነው።

በ12/11/2016  በወቅቱ  የተሳተፉትን ቡድን  ለማስታወስ ያህል ስቮልቫር(Svolvær) ቬስትቮጋይ Vestvågøy ሎዲንገን Lødingen
በውድ ድሩ ወቅት ሶስቱ ሙታኮች Mottak ቡድኖቻቸውን በሁለት ግሩፕ በመክፈልGroup1 and Group2 በማለት ለውድድር እንዳቀረቡ የሚታወስ ነው በዛም ወቅት የስቮልቫር ሙታክ አብዛኛውን ጨዋታ እንዳሸነፈ የሚታውቅ ነው። 2016 SVOLVÆR TEAM PICTURE





 ወደ ትላንትናው ውድድር ስመለስ የተፎካካሪያችን ቡድኖች ቬስትቮጋይ VESTVÅGØY ባለፈው በ12/11/2016 እንዳሰለፈው ቡዱኑን በሁለት ግሩፕ በመክፈል ለውድድር አቅርቦል።

ውድ ድሩን በ አዲስ መልክ በመቀላቀል የተሳተፈው ዕድምያቸው ከ18ዓመት በታችየሆንቱን Under the age የቢሮ ሰራተኞች ቲም SVOLVÆR EM ANSATTE ከፍተኛ ግምት ከተሰጠው ቡድን አንዱ ነበር በተለይም በጠንካራ የኳስምትና የቦታ አሰላለፍ ጥሩ ተፎካካሪ ሆነው መልካም ጨዋታ አሳይተውን በሶስተኛ ደረጃነት በመውጣት ውድድሩን ፈፅመዋል።

ስቮልቫር በሶስት ግሩፕ በመከፈል ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ ነው የቀረበው።
 የመዝጊያው ጨዋታ የተካሄደው የሁለቱ የቡድን መሪዎች/አሰልጣኞች በስብሰባ በመሰማማት ከየግሩፑ ጥሩ የኳስ ብቃት 
አላቸው ብለው የመኑባቸውን ተጨዋቾችን በመምረጥ Beast player  በማቅረብ ከፍተኛ ወሳኝ እልህ የተቀላቀለበት ፉክክር በማድረግ እንደሚታወቀው በውድድር ሕግ የተሻልወና የበለጠው አሸናፊ ዋንጫውን ከፍ አድርጎ እንደሚስመው አይበገሪ አንበሳዎቹ The Lion Svolvær በአማረና የተመልካችን ቀልብ በመመሰጥ ያጠናቀቀው የኖርዌይ እግርኳስ ማሀበርNORGES FOTBALL FORBUND(THE FOOTBALL ASSOCITION OF NORWAY)(FAN) ያዘጋጀውን የወርቅ ሜዳልያ Mr Per Arne  በመሸለም አንገቱ ላይ አጥልቋል።3/12/2016 SVOLVÆR TEAM PICTURE




 በውድድሩ ወቅት ከተለያዩ ሀገሮች በስደት ኖርዌይ የሚኖሩ ተጨዋቾች በግልም ሆነ በቡድን ብቃታቸውን ያሳዩና ያስመሰከሩ
ወደፊትም ከፍተኛ ተስፋ የሚጣል ባቸው ታዳጊዎችም ጠንካራ ተጫዋቾችን አይተናል ይህ ደግሞ ትኩረት ተሰጥቶት
ደጋፊና በተለያየ አቅም የሚረዳቸው የሚንከባከባቸው ሰዎች ካገኙ ለሚረዳቸው አካልም ለግላቸውም በኳስ ጥበብ
ከፍተኛ ቦታ ይደርሳሉ።   Team VESTVÅGØY Picture 3-0 የተሸነፈው

በመጨረሻ ወደኔ ስመጣ ኳስ በመጫወት ቡድን በማሰባሰብና ፣በመስራት፣በመምራት ፣በመምረጥ አቅሜ የፈቀደውን
አስተዋፆኦ አበርክቻለው አድርጊያለው።

ከሁሉም በላይ ላመሰግን የምፈልገው ለዝግጅቱ መሳካት ሀላፊነቱን የወሰደውን አካል ወይም Sponsor የሆነን 
በዋንነት ለውጤቱ ማማርና መሳካት ከፍተኛ ጉልበታቸውን እና የኳስ ክህሎታቸውን ላሳዩን የተለያዩ ሀገሮች ዜግነት
ያላቸውን የ2016 የስቮልቫር ሙታክ ቡድን ወንድሞቼን የከበረ ልባዊ ምስጋናይኔ ከአንገቴ ጎንበስ በማለት አቀርባለው።
befiker09@gmail.com


Monday, September 19, 2016

ከቀድሞው የኢትዮጵያ የሀገር የመከላከያና የፖሊስ ሠራዊት አርበኞች ማህበር የተላለፈ ወቅታዊ ጥሪ


እኛ የቀድሞው የኢትዮጵያ የሀገር የመከላከያና የፖሊስ ሠራዊት ዓባላት ለአለፉት 25 ዓመታት በውድ የሃገራችን ሕዝብ ላይ በወያኔ ህውሃት መራሹ ቡድን እየተፈፀመ ያለውን ሰቆቃ ከሕዝባችን ጋር እየተመለከትን እስካሁን ዘልቀናል። ይሁን እንጅ የሕዝባችንን ሰቆቃና መከራ፣ ስደትና ዕልቂት ከምንም ባለመቁጠር ይባስ ብለው የሃገሪቷን ልዑላዊነት ለታሪካዊ ጠላቶቻችን አሳልፈው ለመስጠት ሽር ጉድ በማለት ላይ ይገኛሉ።
በኢትዮጵያ የረጅም ታሪክ ውስጥ የሃገሪቷን ዳር ድንበር ለባዕድ አሳልፎ ለመስጠት የተደራደረ መንግስት ታይቶም ተሰምቶም አይታወቅም ፣ ሃገሩንና ድንበሩን እንዲጠብቅ አደራ የተሰጠውም ወታደርና የፖሊስ ሠራዊት የዚህ እኩይ ተግባር ተባባሪ የሆነበት ዘመን አልታየም።
ከሁሉም በላይ የህውሃት አቀንቃኝ ካድሪዎች በየጊዜው ከሚጎነጉኑት የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ የሃገሪቷን ታላላቅ ብሄረሰቦች እርስ በርስ በማናቆር የጥላቻ ዘር በማህከላቸው በመበተን ስልጣኑን ለማራዘም ሁነኛ መሳሪያ አድርጎት ይገኛል።
ምንጭ ዘ-ሐበሻ 

Wednesday, July 20, 2016

የሰሜን ጎንደሩ ታጋይ አንጋው ተገኝ መልዕክት ከቂሊንጦ እስር ቤት – “ካሁን በኋላ ሽንታም አማራ አንባልም”

ቀጣዩ መልዕክት የመጣው በ እስር ላይ ከሚገኘው ታጋይ አንጋው ተገኝ ነው:: ታጋይ አንጋው በአሁኑ ወቅት በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ይገኛል:: የጎንደሩን ሕዝባዊ አመጽ ተከትሎ የሚከተለውን መል ዕክት አስተላልፏል:: እንደወረደ ያንብቡት::
ጀግናው የሰሜን ጎንደር የወልቃይት አማራ ሕዝብ ዘመዶቼ የአባቶችህ ታሪክ መድገምህ ካለሁበት ጠባቡ ክፍል ብንሰማ ቁጭ ብዬ ከጓደኞቼ ጋር አለቀስኩ ጀግናው የሰሜን ጎንደር ሰው ድሮም እናቀዋለን! ወገኔ ባንተ ትግል አሁን ለሀጫም ኣንባል! አሁን ሽንታም አማራ አንባልም! የድሮ ስርዓት ናፋቂ ሲሉን በማዕከላዊ አዋርዶ የሚገርፈን በፍርድ ቤት የምናለቅሰው ኣማራነት ማን እንደሆነ ዛሬ ጎንደር ሄዶ ማየት ይችላል፡፡ የጎንደር ሕዝብ የጀመረው ትግል ድንገት አይደለም ለዘመናት በኣማራ ላይ የታወጀበት የወያኔ እልቂት በሶት ያማጣው ቁጭት ነው፡፡
ቀድሞስ ትግላችን የነበረው ከዚህ ተነስተን አይደለምን? አዎ..ዛሬ ለመራር ትግል የተሰለፈነው እኛ ብቻ አይደለንም፡፡ ሁሉም ወገን ለነጻነት ለክብሩ የአባቶቹን ታሪክ ለመድግም ኣርበኛ ታጋይ ሆኗል፡፡ መላው ኣማራ የነጻነት አሸባሪ ተብሏል፡፡ በዚህ ግቢ ውስጥ ከሰሜን ጎንደር የመጣ ከ300 በላይ የኣካባቢው ተወላጅ ልቡ እናተው ዘንድ ይገኛል፡፡ በአማራ ስም እየነገደ የትግሬን የበላይነት የሚያስጠብቅ (ብአዴን) እደተጠበቀው ለህውሃት ያለው ሎሌነቱንና ታማኝነት ለአማራ ሕዝብ ያለውን ጠላትነትና ደም መጣጭነቱን በኣደባባይ በመግለጫው አረጋግጧል። የአማራ ሕዝብ ዛሬ በአንድነት ቆሞ ይህንን አስቸጋሪ ወቅት በብቃት መመከት ካልቻለ እንደትላንቱ የትውልዱን ጀግኖች በወራሪ አስበልቶ መቀመጥ ቀጣዩ ትውልድ ሀገር አለን ማለት አይታሰብም፡፡
ወገኔ ልብ በል በገዛ ሀገራችን እየተፈናቀልን ስንሰደድ ቆይተናል፡፡ ተፈጥሮ የለገሰን ርስታችን ተነጥቆ የጥቂት ቡድን የበዬ ተመልካች አድርገውናል፡፡ ተወልደን ባደግንበት ምድር ከፊት በህወሓት ሰራዊት ከጀርባች በሱዳን ድርቡሽ እያስገደሉን ሲጨፍሩ ብዙ ታዝበናል፡፡ አሁን ግን ነገሩ ተለውጧል እየገደሉ ማንቧረቅ እንግዲህ አበቃ… መሞትም እንዳለ ጀግናው ጎንደሬ ገድሎና ሞቶ አሳይቷል፡፡ ይሄን ሕዝብ አትነካኩት ብለን መክረን ነበር ሆኖም ግን የሚሰማን ጠፍቷል፡፡ እንግዲህ መንገዱን ለነሱም ጨርቅ ያድርግላቸው፡፡ አሁን የጎበዝ አለቃ ሁሉም አለው..ወገን አንድ ነገር መናገር እፈልጋለሁ፡፡
በተለይ የብአዴን አባላትና ደጋፊዎች የአማራን ሕዝብን በሥሙ እያስተዳደሩ በጥቂት ወረበላ ሲገደል ቆሞ ማየት ነገ የልጅ ልጆቻችሁ በኣማራ ምድር የታሪክ ውዳቂ ሆኖ እንደሚቀሩ መገንዘብ ያለባቸው ወሳኝ ጊዜ አሁን ነው፡፡ ይሄን ታላቅነት የሚመጥን የእዉቀትና የስነልቦና ልዕልና የተላበሰ የብአዴን አባል ስለመኖሩ በእርግጥ እጠራጠራለዉ፡፡ ግን ነገ ታፍሩበታላችሁ ይልቅ ከተበደለው በየጊዜው ከሚሞተው ምስኪኑ ወገናችሁ ጎን በመሰለፍ ታሪክ ስሩ መላው የአማራ ተወላጅ በውጪም በውስጥም በኣንድነት መቆም ጊዜው ያስገድዳል፡፡ ጎንደር ሲነሳ ጎጃም ወሎ የሸዋ ሰው መነሳት አለበት፡፡ ለሌውም ወገን በጋራ መሰለፍ ያስፈልጋል፡፡ ይሄ የነጻነት ትግል በሁሉም ስፍራ መቀጣጠል ይኖርበታል፡፡ የአማራ ሕዝብ የመኖር ያለመኖር የህልውና ጉዳይ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡

ድል ለሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ! (ኣንጋው ተገኝ)
ምንጭ (ዘ-ሐበሻ)